ኤርትራ የቀድሞ ሠራዊት አባላትን ለሥልጠና ስትጠራ ዜጎች ከአገር የሚወጡበትን መንገድ አጠበቀች

bdf61e40 f02e 11ef a319 fb4e7360c4ec.jpg

የኤርትራ መንግሥት የቀድሞ የሠራዊት አባላት ወደ የክፍሎቻቸው ለዳግም ሥልጠና እንዲመለሱ እና ሌሎችም ከአገር ለመውጣት የሚጠበቅባቸውን መስፈርቶች እንዳጠበቀ በኤርትራ ውስጥ እና በውጪ ሀገራት የሚገኙ የአገሪቱ ዜጎች ለቢቢሲ አረጋገጡ።

በዚህ መመሪያ መሠረት ከ60 ዓመት በታች የሚገኙ በኤርትራ ሠራዊት ውስጥ ያገለገሉ ዜጎች ተመዝግብው ወደ ማሠልጠኛ እንዲገቡ፤ እንዲሁም ከ50 ዓመት በታች የሆኑ ሰዎች ደግሞ ተገቢውን ፈቃድ ከሚመለከተው የመንግሥት አካል ሳያገኙ ከአገር እንዳይወጡ ያዛል።

ቢቢሲ ትግርኛ ያነጋገራቸው የአሥመራ ከተማ ነዋሪዎች ይህ የኤርትራ መንግሥት ትዕዛዝ በይፋ የተገለጸ አለመሆኑን ተናግረዋል። ነዋሪዎቹ እንደሚያስረዱት ይህ ትዕዛዝ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ያወቁት ከአገር ለመውጣት እና የተለያዩ መንግሥታዊ አገልግሎቶችን ለማግኘት ወደ ቀበሌዎች በሄዱበት ወቅት በኃላፊዎች በተደረገላቸው ገለጻ ነው። Read more

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *